የግርጌ ማስታወሻ
d “እስከ ፍጻሜ ዘመን” የሚለው አባባል “በፍጻሜው ዘመን ውስጥ” ማለትም ሊሆን ይችላል። “እስከ” ተብሎ እዚህ ላይ የተተረጎመው ቃል በአረማይክ ጽሑፍ በዳንኤል 7:25 ላይ ይገኛል። እዚያም ላይ “ውስጥ” እና “ለ” የሚል ትርጉም አለው። ይኸው ቃል በ2 ነገሥት 9:22፤ በኢዮብ 20:5 እና በመሳፍንት 3:26 ላይ በዕብራይስጡ ጽሑፍ ተመሳሳይ ትርጉም አለው። ሆኖም በብዙ ትርጉሞች በዳንኤል 11:35 ላይ “እስከ” ተብሎ ተተርጉሟል። ትክክለኛው አረዳድ ይኸኛው ከሆነ “የፍጻሜው ዘመን” የሚለው የአምላክ ሕዝቦችን ጽናት ፍጻሜ የሚያመለክት መሆን ይኖርበታል። — “ፈቃድህ በምድር ይሁን ” ከተባለው መጽሐፍ ገጽ 286 ጋር አወዳድር።