የግርጌ ማስታወሻ
a አንዳንድ ጊዜ ሃይማኖታዊ መሪዎች ራሳቸው የተዋጉበት ጊዜ አለ። በእንግሊዝ ጦርነት ጊዜ (በ1066) የካቶሊክ አቡን የነበሩት ኦዶ ከሰይፍ ይልቅ መቋሚያቸውን በመጠቀም በጦርነቱ የነበራቸውን ተሳትፎ አሳይተዋል። ደም እስካላፈሰሰ ድረስ አንድ የአምላክ ሰው ሕጋዊ ግድያ መፈጸም ይችላል ብለውም ተናግረዋል። ይህ ከሆነ ከአምስት መቶ ዘመን በኋላ ካርዲናል ኪመንስ ራሳቸው ሰሜን አፍሪካን ለመውረር የመጣውን የስፔይንን ጦር መርተዋል።