የግርጌ ማስታወሻ
e ብዙዎች የሉቃስ ዘገባ ከሉቃስ 21:24 ጀምሮ ሌላ ዓይነት ሐሳብ ይገልጻል ይላሉ። ዶክተር ሊየን ሞሪስ እንዲህ ሲሉ አስገንዝበዋል፦ “ኢየሱስ በመቀጠል ስለ አሕዛብ ዘመን ይናገራል። . . . እንደ አብዛኞቹ ምሑራን አስተያየት ከዚህ በኋላ የኢየሱስ ትንቢት የሚያተኩረው የሰው ልጅ በሚመጣበት ጊዜ ላይ ነው።” ፕሮፌሰር አር ጊንስ “የሰው ልጅ መምጣት (ማቴ 24:29–31፤ ማር 13:24–27)” በሚለው ንዑስ ርዕሳቸው ሥር እንዲህ ብለው ጽፈዋል፦ “‘የአሕዛብ ዘመን’ የሚለው አባባል መጠቀሱ ለዚህ አዲስ ርዕስ መግቢያ ሆኖ ያገለግላል። [ሉቃስ] የትኩረት አቅጣጫውን በመቀየር ስለ ኢየሩሳሌም ጥፋት መናገር ያቆምና ወደፊት ስለሚመጣው ዘመን ይገልጻል።”