የግርጌ ማስታወሻ
f ፕሮፌሰር ዎልተር ኤል ሌይፌልድ እንዲህ ብለው ጽፈዋል፦ “የኢየሱስ ትንቢት ሁለት ክፍል አለው ብሎ ማሰብ ይቻላል። እነሱም፦ (1) በቤተ መቅደሱ ላይ የደረሱትን ጨምሮ በ70 ዓ. ም. የተፈጸሙት ነገሮችና (2) ወደፊት ከረዥም ጊዜ በኋላ የሚፈጸሙትና በራእይ መጽሐፍ ውስጥ ከተጠቀሱት አነጋገሮች ጋር ተመሳሳይ በሆኑ ቃላት የተናገራቸው ነገሮች ናቸው።” በጄ አር ደሜሎ የተዘጋጀው ማብራሪያ እንዲህ ይላል፦ “ጌታችን የተናገረው ስለ አንድ ነገር ሳይሆን ስለ ሁለት ነገሮች እንደሆነና የመጀመሪያው ለሁለተኛው ጥላ እንደሚሆንለት ከተገነዘብን ይህንን ታላቅ ንግግሩን ለመረዳት አስቸጋሪ ከሚያደርጉት ነገሮች ውስጥ አብዛኞቹ ይወገዳሉ። . . . በተለይ ‘ስለ አሕዛብ ዘመን’ የሚናገረው [ሉቃስ] 21:24 . . . ኢየሩሳሌም ከጠፋችበት ጊዜ አንስቶ እስከ ዓለም መጨረሻ ድረስ ባለው ጊዜ መሐል ረዥም ዘመን እንዳለ በግልጽ ያሳያል።”