የግርጌ ማስታወሻ
a መጽሐፍ ቅዱሳዊና ታሪካዊ ማስረጃዎች እንደሚያመለክቱት ኢየሱስ ክርስቶስ የተወለደው በ2 ከዘአበ ነው። ስለዚህ ብዙዎች ከክርስቶስ ልደት በፊት እና በኋላ እየተባሉ የሚጠሩትን ጊዜያት ይበልጥ ግልጽ በሆነ መንገድ ለማስቀመጥ ሲሉ እዘአ (እንደ ዘመናችን አቆጣጠር) እና ከዘአበ (ከዘመናችን አቆጣጠር በፊት) ማለትን ይመርጣሉ። በመጠበቂያ ግንብ ማኅበር ጽሑፎች ላይ የሚጠቀሱት ቀናት የሚገለጹትም በዚህ መንገድ ነው።