የግርጌ ማስታወሻ
a ይሁን እንጂ ይሖዋ ይህ ሰው ይቅርታ ሊደረግለት ይገባል ወይም አይገባም ብሎ ሲወስን ግምት ውስጥ የሚያስገባቸው ሌሎች ነገሮችም አሉ። ለምሳሌ ያህል አንድ መጥፎ ድርጊት የፈጸመ ሰው የአምላክን የአቋም ደረጃዎች የማያውቅ ከሆነ የኃጢአቱን ሸክም ሊቀንስለት ይችላል። ኢየሱስ የገደሉትን ሰዎች አባቱ ይቅር እንዲላቸው በጠየቀ ጊዜ የሰቀሉትን የሮማ ወታደሮች ማለቱ እንደነበረ ግልጽ ነው። “የሚያደርጉትን አያውቁም” ነበር፤ እርሱ በእርግጥ ማን እንደሆነ አላወቁም። ከግድያው በስተጀርባ የነበሩት ሃይማኖታዊ መሪዎች ግን የበለጠ በደል ፈጽመዋል። ከእነርሱ መካከል ብዙዎቹ ይቅርታ ሊያገኙ አይችሉም።—ዮሐንስ 11:45–53ን ከሥራ 17:30 ጋር አወዳድር።