የግርጌ ማስታወሻ
c ይህ አንዳንድ የሕዝበ ክርስትና የእምነት ክፍሎች የፈጸሙት ስሕተት ነው። ሉተራውያን የሚለው ስም የማርቲን ሉተር ጠላቶች ለተከታዮቹ ያወጡላቸው ቅጽል ስም ነበር፤ ተከታዮቹም ተቀበሉት። በተመሳሳይም መጥምቃውያን ውኃ ውስጥ በማጥለቅ የሚደረገውን ጥምቀት ስለሚሰብኩ የእምነቱ ተከታዮች ያልሆኑ ሰዎች ይህን ቅጽል ስም አወጡላቸው፤ እነሱም ተቀበሉት። ከዚህ ጋር በሚመሳሰል መንገድ ሜቶዲስቶች አንድ ሜቶዲስት ያልሆነ ሰው ያወጣላቸውን ስም ተቀብለዋል። ዘ ወርልድ ቡክ ኢንሳይክሎፔድያ ዘ ሶሳይቲ ኦቭ ፍሬንድስ ለምን ኩዌከርስ (አንቀጥቃጮች) እንደተባሉ ሲናገር እንዲህ ይላል፦ “ኩዌከር የተባለው ቃል ፎክስን [የሃይማኖቱን መሥራች] ለመስደብ የተነገረ ቃል ነው፤ ፎክስ አንድን የእንግሊዝ ዳኛ ‘በጌታ ቃል ተንቀጥቀጥ’ ብሎት ነበር። ዳኛው ፎክስን ‘ኩዌከር’ ብሎ ሰየመው።”