የግርጌ ማስታወሻ
a ከእስራኤል ውጪ ይኖሩ የነበሩት ብዙ አይሁዳውያን የዕብራይስጥ ቋንቋን አቀላጥፎ የማንበብ ችሎታቸው እየተዳከመ በመሄዱ በግብጽ በአሌክሳንድሪያ ከተማ እንዳሉት የመሳሰሉ የአይሁዳውያን ማኅበረሰቦች ዕለታዊ መነጋገሪያቸው ወደ ሆነው ቋንቋ የተተረጎመ መጽሐፍ ቅዱስ እንደሚያስፈልጋቸው ተገነዘቡ። ይህንን ፍላጎት ለማሟላት የግሪኩ ሴፕቱጀንት ትርጉም በሦስተኛው መቶ ዘመን ከዘአበ ተዘጋጀ። ይህ ትርጉም ከጊዜ በኋላ ጽሑፎችን ለማወዳደር የሚረዳ ጠቃሚ የመረጃ ምንጭ ሊሆን ችሏል።