የግርጌ ማስታወሻ
b በ760 እዘአ ገደማ ካራይታውያን በመባል የሚታወቅ አንድ የአይሁድ ቡድን ቅዱሳን ጽሑፎችን በጥብቅ እንከተል የሚል ጥያቄ አቀረበ። የረቢዎችን ሥልጣን፣ ‘በቃል የሚተላለፈውን ሕግና’ ታልሙድን ገሸሽ በማድረግ የመጽሐፍ ቅዱስን ጽሑፎች ሥርዓት ባለው ሁኔታ የሚጠብቁበት ትልቅ ምክንያት ነበራቸው። ከዚህ ቡድን መካከል የሆኑ አንዳንድ ቤተሰቦች የተካኑ የማሶሬቲክ ገልባጮች ሆነዋል።