የግርጌ ማስታወሻ
a ኢየሱስ የተናገራቸውን ቃላት እውነተኝነት ለማጥበቅ ብሎ የተጠቀመባቸው ልዩ አገላለጾች በወንጌል ውስጥ ከ70 በሚበልጡ ቦታዎች ላይ ተመዝግበዋል። ብዙውን ጊዜ አንድ ዓረፍተ ነገር መናገር ሲጀምር “አሜን” (“እውነት” በአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ) ይላል። ከዚህ ጋር የሚመሳሰለው የዕብራይስጥ ቃል “የማያጠራጥር፣ እውነት” ማለት ነው። ዘ ኒው ኢንተርናሽናል ዲክሽነሪ ኦቭ ኒው ቴስታመንት ቲኦሎጂ የተባለው መዝገበ ቃላት እንዲህ ብሏል፦ “ኢየሱስ ንግግሩን አሜን ብሎ በመጀመር የሚናገራቸው ነገሮች እርግጠኛና እምነት የሚጣልባቸው እንደሆኑ አሳይቷል። በተናገራቸው ቃላት ከመጽናቱም በላይ ራሱም ሆነ አድማጮቹ እንዲያከብሯቸው የሚያስገድዱ አድርጎ አቅርቧቸዋል። የተናገራቸው ቃላት ያለውን ታላቅነትና ሥልጣን የሚያሳዩ ናቸው።”