የግርጌ ማስታወሻ
a ዘ ኢንተርናሽናል ስታንደርድ ባይብል ኢንሳይክሎፔድያ እንዲህ በማለት ይገልጻል፦ “ሴቶች ከወንዶች እንግዶች ጋር ምግብ አይበሉም ነበር፤ ወንዶች ከሴቶች ጋር መነጋገር የለባቸውም ይባል ነበር። . . . በተለይ በአደባባይ ከሴት ጋር መነጋገር ነውር ነበር።” የረቢዎችን ትምህርቶች የያዘው የአይሁዶች ሚሽና እንዲህ በማለት ይመክራል፦ “ከሴት ጋር ብዙ አታውራ። . . . ከሴት ጋር ብዙ የሚያወራ ሰው በራሱ ላይ ጉዳት ያመጣል፣ የሕጉን ጥናት ችላ ይላል በመጨረሻም ገሃነም ይገባል።”—አቦት 1:5