የግርጌ ማስታወሻ
a ያዕቆብ ቤተሰቡን ከከነዓናውያን ተጽዕኖ ለመጠበቅ ሲል ከዚህ በፊት ጥብቅ እርምጃዎችን እንደወሰደ ሊታወቅ ይገባል። መሠዊያ ሠርቷል፤ ይህ መሠዊያ ከከነዓናውያን ጎረቤቶቹ የሚለየው ዓይነት አሠራር እንዳለው አያጠራጥርም። (ዘፍጥረት 33:20፤ ዘጸአት 20:24, 25) በተጨማሪም ከሴኬም ከተማ ውጪ የሰፈረ ከመሆኑም በላይ የራሱን የውኃ ጉድጓድ ቆፍሮ ነበር። (ዘፍጥረት 33:18፤ ዮሐንስ 4:6, 12) በዚህ የተነሳ ያዕቆብ ከከነዓናውያን ጋር ቅርርብ እንድትመሠርት እንደማይፈልግ ዲና አሳምራ ታውቅ ነበር።