የግርጌ ማስታወሻ
a “ይህ ትውልድ” በሚለው አገላለጽ ውስጥ የገባው ሆቶስ የሚለው አመልካች ተውላጠ ስም “ይህ” ከሚለው የአማርኛ ቃል ጋር በጥሩ ሁኔታ ይስማማል። በዚያን ወቅት እየተፈጸመ ያለን ነገር ወይም ከተናጋሪው ፊት ያለን ሁኔታ ሊያመለክት ይችላል። ቢሆንም ሌላ ትርጉም ሊኖረውም ይችላል። ኤክሰጄቲከል ዲክሽነሪ ኦቭ ዘ ኒው ቴስታመንት (1991) እንዲህ ይላል፦ “[ሆቶስ] የሚለው ቃል በቅርቡ የሚፈጸም ሁኔታን ያመለክታል። በዚህ መሠረት [ኤዎን ሆቶስ] ‘አሁን ያለው ዓለም’ ማለት ሲሆን . . . [ጄኒያ ሆቴ] ደግሞ ‘አሁን ያለው ትውልድ’ ማለት ነው። (ለምሳሌ ማቴ. 12:41 የግርጌ ማስታወሻ፣ 45፤ 24:34 . . .)” ዶክተር ጆርጅ ቢ ዊነር እንዲህ ሲሉ ጽፈዋል፦ “[ሆቶስ] የሚለው ተውላጠ ስም አንዳንድ ጊዜ በአካባቢው ያለውን ሳይሆን ቀደም ብሎ የተጠቀሰውን ጸሐፊው በአእምሮው ውስጥ በመጀመሪያ ደረጃ ለያዘው ዋና ባለቤት በሐሳብ የሚቀርበውን ስም ያመለክታል።”—ኤ ግራመር ኦቭ ዘ ኢድየም ኦቭ ዘ ኒው ቴስታመንት 7ኛ እትም፣ 1897