የግርጌ ማስታወሻ
a ወዲያው ፊዴ ዲፌንሶር (የእምነት ጠበቃ) የተባለው ስም በአገሪቱ ሳንቲሞች ላይ መታተም ጀመረ። ሄንሪ ይህ ስም ለተተኪዎቹ እንዲሰጥ ጠየቀ። ይህ ቃል በአሁኑ ጊዜ በእንግሊዝ ሳንቲሞች ላይ ከገዢው ምስል በላይ ፊድ ደፍ ወይም ኤፍ ዲ በሚል ምሕጻረ ቃል ተጽፎ ይገኛል። በዚህ ምክንያት ለንጉሥ ጄምስ መታሰቢያ ተብሎ በ1611 በታተመው የኪንግ ጄምስ ቨርሽን ላይ “የእምነት ተከላካይ” የሚለው ስም መጻፉ ትኩረት የሚስብ ነው።