የግርጌ ማስታወሻ
c አንዱ ማስረጃ 19 ጊዜ በቀጥታ ተጽፎ ወይም በምሕጻረ ቃላት ተቀምጦ የሚገኘውን “ስሙ” የሚለውን የዕብራይስጥ አገላለጽ የያዘ መሆኑ ነው። ፕሮፌሰር ሀዋርድ እንዲህ ሲሉ ጽፈዋል፦ “አንድ አይሁዳዊ ተከራካሪ በክርስቲያን ጽሑፍ ውስጥ መለኮታዊውን ስም መጥቀሱ የሚያስደንቅ ነገር ነው። ይህ ከግሪክ ወይም ከላቲን የተተረጎመ የዕብራይስጥ ትርጉም ቢሆን ኖሮ ማንም በጽሑፉ ውስጥ አዶናይ [ጌታ] የሚለውን እንጂ በቃላት ሊነገር የማይችለውን መለኮታዊ ስም የሚያመለክቱትን የሐወሐ የተባሉ ፊደላት አገኛለሁ ብሎ ሊጠብቅ አይችልም ነበር። . . . በቃላት ሊገለጽ የማይችለውን ይህን ስም የጨመረው እሱ ነው ብሎ ማሰብ ፈጽሞ የማይቻል ነገር ነው። ሼምቶብ የነበረው የማቴዎስ መጽሐፍ ቅጂ መለኮታዊውን ስም የያዘ እንደነበረና ስሙን ከመጽሐፉ ውስጥ በማውጣት ተጠያቂ ከመሆን ይልቅ እንዳለ ማስቀመጡን መርጦ ሊሆን እንደሚችል ማስረጃዎቹ በግልጽ ያሳያሉ።” ባለ ማጣቀሻው የአዲሲቱ ዓለም ትርጉም መለኮታዊውን ስም በክርስቲያን ግሪክኛ ቅዱሳን ጽሑፎች ውስጥ የሚጠቀምበትን ምክንያት ሲያስረዳ ሼምቶብ ያዘጋጀውን የማቴዎስ ጽሑፍ (J2) ማስረጃ አድርጎ ይጠቅሳል።