የግርጌ ማስታወሻ
a ዛሬ ያለው የአይሁድ እምነት ይህን የመሰለ መልክ እንዲኖረው ፈሪሳውያን ያሳደሩት ተፅዕኖ በቀላሉ የሚገመት ባለመሆኑ ዛሬም ብዙ ገደቦች ከተጨማመሩበት የሰንበት ሕግ ማምለጫ ቀዳዳ መፈላለጋቸው አያስገርምም። ለምሳሌ ያህል በሰንበት ቀን የአክራሪ አይሁዳውያንን ሆስፒታል የሚጎበኝ አንድ ሰው ተጠቃሚዎች የአሳንሱሩን ቁልፍ በመጫን እንደ ኃጢአት የሚቆጠር “ሥራ” እንዳይሠሩ ሲባል አሳንሱሩ ራሱ በየፎቁ እንደሚቆም ይገነዘባል። አንዳንድ አክራሪ የአይሁድ እምነት ተከታይ የሆኑ ዶክተሮች የመድኃኒት ትእዛዞችን የሚጽፉት ቀለሙ ከጥቂት ቀናት በኋላ በሚለቅ ብዕር ነው። ለምን? ሚሽና መጻፍን ከ“ሥራ” የሚመድበው ቢሆንም “መጻፍ” ማለት ዘላቂ ምልክት መተው ማለት ነው ብሎ ስለሚያብራራ ነው።