የግርጌ ማስታወሻ
a የአምላክ መንፈስ በመጀመሪያው መቶ ዘመን ክርስቲያኖች ላይ ካከናወናቸው ዋና ዋና ነገሮች አንዱ የአምላክ መንፈሳዊ ልጆችና የኢየሱስ ወንድሞች አድርጎ መቀባት ነው። (2 ቆሮንቶስ 1:21, 22) ይህ ለ144,000 የክርስቶስ ደቀ መዛሙርት ብቻ የተወሰነ ነው። (ራእይ 14:1, 3) በዛሬው ጊዜ አብዛኞቹ ክርስቲያኖች በምድር ላይ በገነት ለዘላለም የመኖር ተስፋ በደግነት ተሰጥቷቸዋል። ቅቡዓን ባይሆኑም እንኳ እነርሱም የአምላክን ቅዱስ መንፈስ እርዳታና ማጽናኛ ያገኛሉ።