የግርጌ ማስታወሻ
b በዕብራውያን 12:1 ላይ “ምሥክሮች” ተብሎ የተተረጎመው ቃል ማርታይስ ከሚል የግሪክ ቃል የመጣ ነው። በቨስት የተዘጋጀው የግሪክኛውን አዲስ ኪዳን ፍቺ መመርመር (Word Studies From the Greek New Testament) የተባለ መጽሐፍ በሰጠው ፍቺ መሠረት “በማንኛውም መንገድ ይሁን ያየውን፣ የሰማውን ወይም የሚያውቀውን የሚመሠክር ወይም መመሥከር የሚችል” የሚል ትርጉም አለው። በናይጀል ተርነር የተዘጋጀው ክርስቲያናዊ ቃላት (Christian Words) የተባለው መጽሐፍ የቃሉ ትርጉም “ከራሱ ተሞክሮ በመነሳትና በእውነት እንዲሁም በያዘው አመለካከት ላይ ባለው የጸና እምነት ላይ ተመሥርቶ” የሚናገር ማለት ነው ይላል።