የግርጌ ማስታወሻ
a በአንድ ወቅት መጠበቂያ ግንብ የሚከተለውን አስተዋይነት የተሞላበት አስተያየት ሰንዝሮ ነበር:- “ሕይወታችንን ከንቱ ነገሮችን በማሳደድ ልናሳልፈው አይገባም፤ . . . ሕይወት ይህ ብቻ ከሆነ ሁሉ ነገር ከንቱ ነው ማለት ነው። ይህ ሕይወት ወደ አየር ተወርውሮ ተመልሶ ትቢያ ላይ እንደሚወድቅ ኳስ ነው። ታይቶ እንደሚጠፋ ጥላ፣ እንደሚረግፍ አበባ፣ ሲቆረጥ ወዲያው ጥውልግ እንደሚል ቅጠል ነው። . . . የሕይወታችን ርዝማኔ በዘላለማዊነት ሚዛን ስትለካ ከቁጥርም የማትገባ ቅንጣት ነች። በዘመናት ጅረት ውስጥ እንደ አንድ ጠብታ እንኳን አትሆንም። በእርግጥም [ሰሎሞን] በሕይወት ውስጥ ያሉትን ብዙ ሰብዓዊ ፍላጎቶችና የሥራ እንቅስቃሴዎች ከገመገመ በኋላ ከንቱ ናቸው ማለቱ ትክክል ነው። ሕይወታችን በቅጽበት ያልፋል፤ መወለዳችን ምንም ፋይዳ ያለው አይመስልም፤ ወደፊትም ተወልደው ከሚሞቱት በቢልዮን የሚቆጠሩ ሰዎች መካከል ጭራሽ በሕይወት እንደነበርን እንኳን የሚያውቁት እጅግ በጣም ጥቂት ናቸው። ይህ አፍራሽ አስተሳሰብ የተጠናወተው ወይም ተስፋ የቆረጠ ሰው አስተያየት አይደለም። ሕይወት ይህ ብቻ ከሆነ ይህ አስተያየት እውነት ነው፤ ልንቀበለው የሚገባ ሐቅና እውነታውን መሠረት ያደረገ አመለካከት ነው።”— ነሐሴ 1, 1957 ገጽ 472