የግርጌ ማስታወሻ
c በ1267 ናክማንዲዝ አሁን እስራኤል ተብላ ወደ ምትጠራው አገር ሄደ። በሕይወቱ የመጨረሻ ዓመታት ብዙ ነገሮችን አከናውኗል። አይሁዶችን እንደገና ከማቋቋሙም በላይ በኢየሩሳሌም አንድ የጥናት ማዕከል መሥርቷል። የመጀመሪያዎቹን አምስት የመጽሐፍ ቅዱስ መጽሐፍት ማለትም ቶራህን የሚያብራራ ጽሑፍ ከማዘጋጀቱም በተጨማሪ ሰሜናዊ የጠረፍ ከተማ በሆነች በኤክሬ የአይሁድ ማኅበረሰብ መንፈሳዊ መሪ ሆኖ አገልግሏል፤ በ1270 በዚህች ከተማ ሞተ።