የግርጌ ማስታወሻ
a ኢየሱስ ለትርፍ የሚደረገውን ሩጫ ለማስቆም ቆራጥ እርምጃ ወስዷል። አንድ ታሪክ ጸሐፊ እንደገለጹት የቤተ መቅደሱ ቀረጥ መከፈል የነበረበት የተወሰነ ዓይነት ባለው የጥንት የአይሁዳውያን ሣንቲም ብቻ ነበር። በመሆኑም ወደ ቤተ መቅደሱ የሚመጡ ብዙ ጎብኚዎች ቀረጡን መክፈል ይችሉ ዘንድ ገንዘባቸውን መለወጥ ያስፈልጋቸው ነበር። ገንዘብ ለዋጮቹ የተወሰነ መጠን ያለው ክፍያ እንዲጠይቁ ፈቃድ ስለነበራቸው ብዙ ገንዘብ ያገኙ ነበረ።