የግርጌ ማስታወሻ
a አንዳንድ ትርጉሞች የአምላክን ሕዝቦች የሚነካ የአምላክን ዓይን እንደሚነካ ሳይሆን የእስራኤልን ወይም የራሱን ዓይን እንደሚነካ አስመስለው ተርጉመውታል። ይህ ስህተት የተፈጠረው በመካከለኛው ዘመን በኖሩትና ተቃራኒ ሐሳብ ያስተላልፋሉ ያሏቸውን ጥቅሶች በራሳቸው መንገድ በስህተት ለማስተካከል በሞከሩት ጸሐፊዎች አማካኝነት ነው። ይህን ማድረጋቸው ይሖዋ ያለው የአዛኝነት ስሜት እንዲሠወር አድርጓል።