የግርጌ ማስታወሻ
b እነዚህ ሳንቲሞች እያንዳንዳቸው አንድ አንድ ሌፕተን ሲሆኑ በወቅቱ ይሠራባቸው ከነበሩት የአይሁዳውያን ሳንቲሞች ሁሉ የመጨረሻዎቹ ትንንሽ ሳንቲሞች ናቸው። የሁለት ሌፕታ ዋጋ የአንድ ቀን ምንዳ 1/64ኛ ነው። እንደ ማቴዎስ 10:29 ገለጻ አንድ ሰው በአንድ አሳሪዮን ሳንቲም (ይህ ከስምንት ሌፕታ ጋር የሚተካከል ነው) ሁለት ድንቢጦች መግዛት ይችል ነበር፤ እነዚህ፣ ድሃ የሆኑ ሰዎች ለመብል የሚጠቀሙባቸው በጣም ርካሽ ወፎች ናቸው። ይህቺ መበለት ግን የነበራት ገንዘብ ለአንድ ጊዜ ምግብ እንኳ የማትበቃውን አንዲት ድንቢጥ ለመግዛት ከሚያስችለው ዋጋ ግማሽ ያህል ብቻ ነበር። በእርግጥም ይህች ሴት ድሃ ነበረች።