የግርጌ ማስታወሻ
b ጳውሎስ በሮም ለሁለተኛ ጊዜ ታሥሮ በነበረበት ወቅት ጢሞቴዎስ “መጻሕፍቱን ይልቁንም በብራና የተጻፉትን” እንዲያመጣለት ጠይቆት ነበር። (2 ጢሞቴዎስ 4:13) ጳውሎስ በእሥር ቤት ሳለ ማጥናት ይችል ዘንድ እንዲያመጣለት የጠየቀው የዕብራይስጥ ቅዱሳን ጽሑፎችን ክፍል ሳይሆን አይቀርም። “ይልቁንም በብራና የተጻፉትን” የሚለው መግለጫ በፓፒረስም በብራናም የተጻፉ ጥቅልሎች እንደነበሩ የሚጠቁም ሊሆን ይችላል።