የግርጌ ማስታወሻ
a አንዳንድ ተመራማሪዎች ይሁዳ ጠቅሶ የጻፈው መጽሐፈ ሄኖክ ከተባለው የአዋልድ መጽሐፍ ነው በማለት ይከራከራሉ። ይሁን እንጂ አር ሲ ኤች ሌንስኪ እንዲህ ብለዋል:- “‘መጽሐፈ ሄኖክ የተባለው መጽሐፍ ምንጩ ከየት ነው?’ ብለን እንጠይቅ ይሆናል። መጽሐፉ ባዕድ ጭማሪ ሲሆን የተለያዩ ክፍሎች መቼ እንደተጻፉ በእርግጠኝነት የሚያውቅ ማንም የለም። . . . ምናልባት አንዳንዶቹ መግለጫዎች ከራሱ ከይሁዳ አልተወሰዱ ይሆናል፤ ሆኖም ማንም ሰው እንዲህ ብሎ በእርግጠኝነት ሊናገር አይችልም።”