የግርጌ ማስታወሻ
b ብሪታኒያዊው ምሁር ጂ አር ቢዝሊ-መርኢ እንዲህ ብለዋል:- “‘ይህ ትውልድ’ የሚለው ሐረግ በትርጉም ረገድ ምንም ዓይነት ችግር ሊፈጥር አይገባም። በጥንቱ ግሪክ ዬኔአ ማለት ልደት፣ ተወላጆች ብሎም ዘር የሚል ትርጉም ስላለው [በግሪክኛው ሴፕቱጀንት] ላይ አብዛኛውን ጊዜ . . . እድሜ፣ የሰው ልጅ እድሜ ወይም በአንድ ወቅት የሚኖሩ ሰዎችን ትውልድ የሚያመለክተውን ዶር የሚለውን የዕብራይስጥ ቃል ለመተርጎም አገልግሏል። . . . ኢየሱስ ተናግሯቸዋል በሚባሉ ሐሳቦች ላይ ቃሉ ድርብ ትርጉም የሚያስተላልፍ ሲሆን በአንድ በኩል በዘመኑ የነበሩ ሰዎችን ለማመልከት ብቻ የተሠራበት ሲሆን በሌላ በኩል ደግሞ ነቀፋ አዘል መሆኑን የሚያሳይ ነበር።”