የግርጌ ማስታወሻ
a አንድ ምሁር እንደተናገሩት ሚክያስ 7:18 ላይ የተሠራበት የዕብራይስጡ ምሳሌያዊ አነጋገር “በሚጓዝበት ጊዜ ትኩረት ሊሰጠው ያልፈለገውን ነገር ምንም ልብ ሳይል እያለፈ ከሚሄድ ተጓዥ ባሕርይ የተወሰደ ነው። እዚህ ላይ ለመግለጽ የተፈለገው አምላክ ኃጢአትን አያስተውልም ወይም አቃልሎ ይመለከታል ወይም ከቁብ አይቆጥርም ለማለት ሳይሆን ለመቅጣት ሲል ሆነ ብሎ በአእምሮው ውስጥ አይዝም ወይም በሌላ አባባል ከመቅጣት ይልቅ ይቅር የሚል መሆኑን የሚያመለክት ነው።”—መሳፍንት 3:26፤ 1 ሳሙኤል 16:8