የግርጌ ማስታወሻ
a ሲ ቲ ራስል ከሞተ በኋላ የሕዝቅኤልንና የራእይን መጻሕፍት ለማብራራት የተሞከረበት የቅዱሳን ጽሑፎች ጥናት ሰባተኛ ጥራዝ የሚል ስያሜ የተሰጠው ጽሑፍ ተዘጋጀ። ይህ ጥራዝ የያዘው ማብራሪያ በከፊል የተመሠረተው ራስል እነዚህን የመጽሐፍ ቅዱስ መጻሕፍት በተመለከተ በሰጠው ሐሳብ ላይ ነበር። ሆኖም የእነዚህን ትንቢቶች ትርጉም ማብራራት የሚቻልበት ጊዜ ገና አልደረሰም ነበር። ስለዚህ የቅዱሳን ጽሑፎች ጥናት በተባለው ጥራዝ ላይ የተሰጠው ማብራሪያ በአጠቃላይ ሲታይ ድንግዝግዝ ያለ ነበር። ዓመታት እያለፉ ሲሄዱ ይገባናል የማንለው የይሖዋ ደግነትና በዓለም ላይ የሚከናወኑ ሁኔታዎች ክርስቲያኖች የእነዚህን የትንቢት መጻሕፍት ትርጉም ይበልጥ በትክክል እንዲረዱ አስችለዋቸዋል።