የግርጌ ማስታወሻ
a የሞቱት ወታደሮችና ሲቪሎች ቁጥር ምን ያህል እንደሆነ በትክክል አይታወቅም። ለምሳሌ ያህል በ1998 የታተመው ፋክትስ አባውት ዚ አሜሪካን ዎርስ የተባለው መጽሐፍ ሁለተኛውን የዓለም ጦርነት በማስመልከት ሲናገር “በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ወቅት 50 ሚልዮን የሚያክሉ (ወታደሮችና ሰላማዊ ሰዎች) እንደሞቱ አብዛኞቹ ምንጮች ይገልጻሉ። ሆኖም ጉዳዩን በቅርብ ያጠኑ በርካታ ምንጮች ትክክለኛው አኃዝ ከፍተኛ እንደሆነና ከዚህ ቁጥር በእጥፍ እንደሚበልጥ ያምናሉ።”