የግርጌ ማስታወሻ
a ሌላም መታለፍ የሌለበት ጉዳይ አለ፤ በሜክሲካውያን ናሲምዬንቶ ላይ ያለው ልጅ “ሕፃኑ አምላክ” በሚል የሚታወቅ ሲሆን ይህም ሕፃን ሆኖ ወደ ምድር የመጣው አምላክ ራሱ ነው ከሚለው ሐሳብ የመነጨ ነው። ይሁን እንጂ መጽሐፍ ቅዱስ የሚገልጸው ኢየሱስ ምድር ላይ የተወለደ የአምላክ ልጅ መሆኑን ነው። ልክ እንደ ይሖዋ ሁሉን ቻይ አምላክ ወይም ከእሱ ጋር እኩል አይደለም። የዚህን ጉዳይ እውነተኝነት በተመለከተ በሉቃስ 1:35፤ በዮሐንስ 3:16፤ 5:37፤ 14:1, 6, 9, 28፤ 17:1, 3፤ 20:17 ላይ የተሰጠውን ሐሳብ ተመልከት።