የግርጌ ማስታወሻ
a ታቦቱ ማደሪያው ድንኳን ውስጥ ገብቶ ከተቀመጠ በኋላም መሎጊያዎቹ ከቀለበቶቹ ውስጥ አይወጡም ነበር። በዚህም ምክንያት መሎጊያዎቹ ለሌላ ለምንም ዓላማ አይውሉም። በተጨማሪም ታቦቱ በእጅ መነካት አይኖርበትም። መሎጊያዎቹ ከቀለበቶቹ ውስጥ ይወጡ የነበረ ቢሆን ኖሮ ታቦቱን ማጓጓዝ ባስፈለገ ጊዜ ሁሉ መሎጊያዎቹን በቀለበቶቹ ውስጥ ለማስገባት ቅዱስ የሆነውን ታቦት በእጅ መንካት የግድ ይሆን ነበር። በዘኁልቊ 4:6 ላይ ‘መሎጊያዎቹን ስለማስገባት’ የሚናገረው ሐሳብ ክብደት ያለውን ታቦት ወደ አዲስ ሠፈር ተሸክሞ ለማድረስ በቅድሚያ መሎጊያዎቹን ስለ ማዘጋጀት ወይም ስለ ማስተካከል የሚገልጽ ሊሆን ይችላል።