የግርጌ ማስታወሻ
a ጎርደን ዲ ፌ የተባሉ አንድ የመጽሐፍ ቅዱስ ምሁር “ፍቅር ይታገሣል ቸርነትንም ያደርጋል” በማለት ጳውሎስ በሰጠው ሐሳብ ላይ አስተያየታቸውን ሲገልጹ እንዲህ በማለት ጽፈዋል:- “በጳውሎስ መንፈሳዊ ትምህርት መሠረት እነዚህ ባሕርያት [ትዕግሥትና ደግነት] አምላክ የሰው ልጆችን የሚመለከትባቸው ሁለት ገጽታዎች ናቸው። (ከሮሜ 2:4 ጋር አወዳድር።) አምላክ ዓመፀኛ በሆኑት ሰዎች ላይ ቁጣውን ከማውረድ በታቀበ ጊዜ በአንድ በኩል ፍቅራዊ ትዕግሥቱ ታይቷል። በሌላ በኩል ደግሞ ምሕረቱ በተገለጠባቸው በሺህ በሚቆጠሩ ቦታዎች ላይ ደግ መሆኑ ታይቷል። በዚህም የተነሳ ጳውሎስ ስለ ፍቅር ማብራሪያ ሲሰጥ ስለ አምላክ ሁለት መግለጫዎችን ሰጥቷል። አንደኛው በክርስቶስ አማካኝነት ትዕግሥት ማሳየቱንና በሁለተኛ ደረጃ ደግሞ መለኮታዊ የፍርድ ቅጣት ሊቀበሉ ለሚገባቸው ሰዎች ደግ መሆኑን አሳይቷል።”