የግርጌ ማስታወሻ
a ሜምፊቦስቴ አድናቂና ትሑት ሰው ስለነበር ሥልጣን ለማግኘት ሲል እንዲህ ያለ እርምጃ ይወስዳል ብሎ ማመን ያስቸግራል። የአባቱን የዮናታንን የታማኝነት ታሪክ እንደሚያውቅ ምንም ጥርጥር የለውም። ዮናታን የንጉሥ ሳኦል ልጅ የነበረ ቢሆንም እንኳ ይሖዋ በእስራኤል ላይ እንዲነግሥ የመረጠው ዳዊትን እንደሆነ በትህትና አምኖ ተቀብሏል። (1 ሳሙኤል 20:12-17) ዮናታን ፈሪሃ አምላክ የነበረው የሜምፊቦስቴ ወላጅና የዳዊት ታማኝ ወዳጅ እንደመሆኑ መጠን ልጁ ንጉሣዊ ሥልጣን እንዲመኝ አያስተምረውም።