የግርጌ ማስታወሻ
a እዚህ ላይ የተጠቀሱት “ከዋክብት” ቃል በቃል መላእክትን አያመለክቱም። ኢየሱስ አንድን ሰብዓዊ ሰው በመጠቀም በዓይን ለማይታዩ መንፈሳዊ ፍጥረታት መልእክት እንደማያጽፍ የተረጋገጠ ነው። ስለዚህ ‘ከዋክብቱ’ በጉባኤ ውስጥ ያሉትን የኢየሱስ መልእክተኛ እንደሆኑ ተደርገው የተቆጠሩትን ሰብዓዊ የበላይ ተመልካቾችን ወይም ሽማግሌዎችን የሚያመለክቱ መሆን አለባቸው። ቁጥራቸው ሰባት መሆኑ በአምላክ የተወሰነ ሙላትን ያመለክታል።