የግርጌ ማስታወሻ
a አርመናውያን አገራቸውን ከአራራት ተራሮች ጋር የሚያዛምዱበት አንዱ ምክንያት ይህ ነው። በጥንት ጊዜ አርሜኒያ እነዚህ ተራሮች ያሉበትን ቦታ የምታጠቃልል ሰፊ ግዛት ነበረች። በዚህም ምክንያት የግሪክኛው ሴፕቱጀንት የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጉም በኢሳይያስ 37:38 ላይ ያለውን ‘የአራራት አገር’ የሚለውን አባባል “አርሜኒያ” በማለት ተርጉሞታል። በአሁኑ ወቅት የአራራት ተራሮች በቱርክ ውስጥ በምሥራቃዊው ድንበር ላይ ይገኛሉ።