የግርጌ ማስታወሻ
b በአንድ ወቅት ጳውሎስና ሌሎች አራት ክርስቲያኖች ሥርዓቱ በሚጠይቀው መሠረት ራሳቸውን ለማንጻት ወደ ቤተ መቅደስ ሄደው ነበር። በወቅቱ ሕጉ በእነርሱ ላይ የማይሠራ ቢሆንም ጳውሎስ በኢየሩሳሌም ያሉ ሽማግሌዎች የሰጡትን ምክር ተከትሏል። (የሐዋርያት ሥራ 21:23-25) ይሁን እንጂ አንዳንድ ክርስቲያኖች ወደ ቤተ መቅደስ መግባት እንደሌለባቸው ወይም እንዲህ ያለውን ሥርዓት መከተል እንደማይገባቸው ተሰምቷቸው ይሆናል። በዚያ ዘመን እንደነበረው ሁሉ ዛሬም የሰዎች ኅሊና ይለያያል።