የግርጌ ማስታወሻ
a በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ “ጥላቻ” የሚለው ቃል የተለያዩ ትርጉሞች አሉት። በአንዳንድ ቦታዎች ላይ ከሌላው ባነሰ መጠን መውደድ የሚል ትርጉም አለው። (ዘዳግም 21:15, 16) ከዚህ በተጨማሪ “ጥላቻ” የሚለው ቃል አንድ ሰው ጉዳት የማድረስ ዓላማ ባይኖረውም እንኳ አንድን ነገር መጸየፉን ወይም መራቁን ሊያመለክት ይችላል። ይሁን እንጂ “ጥላቻ” የሚለው ቃል የማጥቃት ፍላጎት የታከለበት ሥር የሰደደን የጠላትነት ስሜት ሊያመለክትም ይችላል። በዚህ ርዕስ ውስጥ የምንመረምረው እንዲህ ያለውን ጥላቻ ነው።