የግርጌ ማስታወሻ
b በተጨማሪም ጳውሎስ በአምላክና በመንፈስ በተቀቡት ‘ልጆቹ’ መካከል ስለተመሠረተው አዲስ ዝምድና በሚያብራራበት ጊዜ በሮም ግዛት ውስጥ የሚኖሩ አንባቢዎች ጠንቅቀው የሚያውቁትን ሕግ ነክ ሐሳብ ተጠቅሞ ነበር። (ሮሜ 8:14-17) “ሮማውያን ያልወለዱትን ሰው እንደ ልጃቸው የመቀበል ልማድ ነበራቸው፤ ይህ ልማድ ስለ ቤተሰብ ካላቸው አመለካከት ጋር በቅርብ የተያያዘ ነው” በማለት ሴንት ፖል አት ሮም የተባለው መጽሐፍ ዘግቧል።