የግርጌ ማስታወሻ
a በኤፍ ሲ ኩክ የተዘጋጀው ዘ ሆሊ ባይብል ዊዝ አን ኤክስፕላናቶሪ ኤንድ ክሪቲከል ኮሜንተሪ የተባለው መጽሐፍ በጥንት ዘመን ይደረግ የነበረውን ይህን ዓይነቱን ልማድ አስመልክቶ የሚከተለውን አስፍሯል:- “ሰዎች ውኃ በተሞላ ዋንጫ ውስጥ እንደ ወርቅ፣ ብር ወይም እንቁ ያሉ ነገሮችን በመክተትና ሁኔታውን በማስተዋል አሊያም እንዲሁ ውኃውን እንደ መስታወት በመመልከት ይህን ድርጊት ይፈጽሙ ነበር።” የመጽሐፍ ቅዱስ ምሑር የሆኑት ክሪስተፈር ዎርድስወርዝ “አንዳንድ ጊዜ ዋንጫው በውኃ ከተሞላ በኋላ የፀሐይ ብርሃን ውኃው ላይ ሲያርፍ የሚፈጥረውን ምስል በመመልከት መልስ ይሰጣል” በማለት ተናግረዋል።