የግርጌ ማስታወሻ
a የጥንቷ እስራኤል ንጉሥ የነበረው ዳዊት ኢያቡሳውያንን ድል አድርጎ ምድራዊውን የጽዮን ተራራ በመያዝ ዋና ከተማው አድርጓታል። (2 ሳሙኤል 5:6, 7, 9) ቅዱሱንም ታቦት ወደ ጽዮን አዛውሮታል። (2 ሳሙኤል 6:17) ታቦቱ የይሖዋን መገኘት ያመለክት ስለነበር ጽዮን የአምላክ ማደሪያ እንደሆነች ተደርጋ ተገልጻለች፤ ይህም ለሰማይ ተስማሚ ምሳሌ እንድትሆን አድርጓታል።—ዘፀአት 25:22፤ ዘሌዋውያን 16:2፤ መዝሙር 9:11፤ ራእይ 11:19