የግርጌ ማስታወሻ
a በርካታ የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጉሞች ኤሬትስ የሚለውን የዕብራይስጥ ቃል “ምድር” በማለት ፋንታ “መሬት” ብለው ስለተረጎሙት ብቻ መዝሙር 37:11, 29 ላይ የሚገኘው ኤሬትስ የሚያመለክተው ለእስራኤላውያን የተሰጣቸውን ውስን መሬት ነው ብሎ ማሰብ ምክንያታዊ አይደለም። በዊልያም ዊልሰን የተዘጋጀ ኦልድ ቴስታመንት ዎርድ ስተዲስ የተባለ መጽሐፍ ኤሬትስ ለሚለው ቃል እንዲህ የሚል ፍቺ ሰጥቶታል:- “በደፈናው ሲታይ ቃሉ ሰዎች የሚኖሩበትንም ሆነ የማይኖሩበትን መላውን ምድር የሚያመለክት ሲሆን በአንዳንድ ሁኔታዎች ደግሞ አንድን የተወሰነ የምድር ክፍል፣ መሬት ወይም አገር ለማመልከት ተሠርቶበታል።” በመሆኑም የዕብራይስጡ ቃል ዋነኛ ፍቺ የሚያመለክተው ፕላኔታችንን ወይም መላዋን ምድር ነው።—የጥር 1, 1986 መጠበቂያ ግንብ (እንግሊዝኛ) ገጽ 31ን ተመልከት።