የግርጌ ማስታወሻ
c የአገሩ ሕግ ከዚህ የተለየ መመሪያ እስከሌለው ድረስ የይሖዋ ምሥክሮች አምላክን የሚያስከብረውን የሚከተለውን የጋብቻ መሐላ ይጠቀማሉ። ሙሽራው እንዲህ ይላል:- “እኔ [የሙሽራው ስም] ሁለታችንም በአምላክ የጋብቻ ሥርዓት ሥር በዚች ምድር ላይ በሕይወት አብረን እስከኖርን ድረስ በቅዱሳን ጽሑፎች ላይ ለክርስቲያን ባሎች በተሰጠው መለኮታዊ ሕግ መሠረት አንቺን [የሙሽራዋ ስም] ልወድሽና ልንከባከብሽ ሚስቴ አድርጌ ወስጄሻለሁ።” ሙሽራዋ እንዲህ ትላለች:- “እኔ [የሙሽራዋ ስም] ሁለታችንም በአምላክ የጋብቻ ሥርዓት ሥር በዚች ምድር ላይ በሕይወት አብረን እስከኖርን ድረስ በቅዱሳን ጽሑፎች ላይ ለክርስቲያን ሚስቶች በተሰጠው መለኮታዊ ሕግ መሠረት አንተን [የሙሽራው ስም] ልወድህ፣ ልንከባከብህና በጥልቅ ላከብርህ ባሌ አድርጌ ወስጄሃለሁ።”