የግርጌ ማስታወሻ
a በተመሳሳይም የሃርቫርድ ዩኒቨርሲቲ ባልደረባና የሥነ ፈለክ ተመራማሪ የሆኑት ፕሮፌሰር ኦወን ጂንጅሪች እንዲህ ሲሉ ጽፈዋል:- “ከራስ ወዳድነት ነፃ በሆነ ስሜት ለሌሎች የማሰብ ዝንባሌ፣ እንስሳትን በማጥናት ሳይንሳዊ መልስ ሊገኝለት የማይችል ጥያቄ ያስነሳል። ለጥያቄው ይበልጥ አሳማኝ የሆነ መልስ ማግኘት የሚቻለው ከሌላ አቅጣጫ ሳይሆን አይቀርም። ይኸውም ሕሊናን ጨምሮ የሰው ልጆች ሰብዓዊ ርኅራኄ እንዲሰማቸው ከሚያደርጓቸው አምላክ ከሰጣቸው ባሕርያት ጋር የተያያዘ መሆን አለበት።”