የግርጌ ማስታወሻ
a አስተማማኝ በሆኑት ጥንታዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ቅጂዎች ላይ ቁጥር 44 እና 46 አይገኙም። ምሑራን፣ ሁለቱ ቁጥሮች ከጊዜ በኋላ የተጨመሩ ሊሆኑ እንደሚችሉ ይገልጻሉ። ፕሮፌሰር አርኪባልድ ቶማስ ሮበርትሰን እንዲህ ሲሉ ጽፈዋል:- “ጥንታዊ በሆኑትና ከሁሉ በተሻሉት ቅጂዎች ላይ እነዚህ ሁለት ቁጥሮች አይገኙም። እነዚህ ቁጥሮች የተጨመሩት ከምዕራብና ከሶርያ (ባይዛንታይን) የጥንታዊ ጽሑፎች ቅጂዎች ነው። በቁጥር 48 ላይ ያለውን ሐሳብ የሚደግሙ ናቸው። በመሆኑም ቁጥር 44 እና 46 ትክክለኛ ባለመሆናቸው [አውጥተናቸዋል]።”