የግርጌ ማስታወሻ
b ከዚህ ቀደም በወጣ መጠበቂያ ግንብ ላይ፣ ዘሩ ወደ ጉልምስና ማደግ የሚያስፈልጋቸውን የግለሰብ ክርስቲያኖች ባሕርያት እንደሚያመለክት እንዲሁም በአካባቢያቸው ያሉ የተለያዩ ነገሮች በክርስቲያኖች ባሕርይ ላይ ተጽዕኖ እንደሚያደርጉ ተገልጾ ነበር። ይሁን እንጂ ኢየሱስ በተናገረው ምሳሌ ላይ ዘሩ እንደተበላሸ ወይም ፍሬው እንደበሰበሰ አለመገለጹን ልብ ማለት ያስፈልጋል። ከዚህ ይልቅ ዘሩ ምንም ሳይሆን ወደ ጉልምስና ያድጋል።—የሰኔ 15, 1980 መጠበቂያ ግንብ ገጽ 17-19 (እንግሊዝኛ) እንዲሁም “መንግሥትህ ትምጣ” የተባለውን መጽሐፍ ገጽ 96-99 ተመልከት።