የግርጌ ማስታወሻ
a “ግኖስቲሲዝም” የሚለው ቃል በ2ኛው መቶ ዘመን የተነሳውን በፍልስፍና ላይ የተመሠረተ ሃይማኖታዊ እንቅስቃሴ ያመለክታል። ከግሪክኛ የተወሰዱት “ግኖስቲክ” እና “አፖክሪፋል” የሚሉት ቃላት በቅደም ተከተል “ሚስጥራዊ እውቀት” እና “በጥንቃቄ የተሰወረ” የሚል ትርጉም ሊኖራቸው ይችላል። እነዚህ ቃላት በክርስቲያን ግሪክኛ ቅዱሳን መጻሕፍት ውስጥ ከሚገኙትና የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ለመሆናቸው ተቀባይነት ካገኙት ወንጌሎች፣ የሐዋርያት ሥራ፣ መልእክቶችና ራእዮች ጋር በሚመሳሰል መንገድ የተዘጋጁ የሐሰት ጽሑፎችን ያመለክታሉ።