የግርጌ ማስታወሻ
b ጴጥሮስ እዚህ ላይ ምድር የሚለውን ቃል የተጠቀመበት ምሳሌያዊ በሆነ መንገድ ነው። የመጽሐፍ ቅዱስ ጸሐፊ የነበረው ሙሴም በተመሳሳይ ምድር የሚለውን ቃል በምሳሌያዊ መንገድ ተጠቅሞበት ነበር። “ምድርም ሁሉ በአንድ ቋንቋና በአንድ ንግግር ነበረች” ሲል ጽፏል። (ዘፍጥረት 11:1 የ1954 ትርጉም) ግዑዟ ምድር “አንድ ቋንቋ” እንደማትናገር ሁሉ የምትጠፋውም ግዑዟ ምድር አይደለችም። ከዚህ ይልቅ ጴጥሮስ እንደተናገረው ጥፋት የሚደርስባቸው ፈሪሃ አምላክ የሌላቸው ሰዎች ናቸው።