የግርጌ ማስታወሻ
b ይህ ቅዱስ ማደሪያ አራት ማዕዘን ቅርጽ ያለው ሲሆን በእንጨት አውታር ላይ የተዘረጋ ትልቅ ድንኳን ነበር። ድንኳኑ የተሠራው ምርጥ በሆኑ ቁሳቁሶች ይኸውም በአቆስጣ ቆዳ፣ ውብ በሆነ መንገድ በተጠለፉ ጨርቆች እንዲሁም በብርና በወርቅ በተለበጡ ውድ እንጨቶች ነበር። ይህ ቅዱስ ድንኳን የሚገኘው አራት ማዕዘን ቅርጽ ባለው ግቢ ውስጥ ሲሆን በግቢው ውስጥ የሚያምር መሠዊያም አለ። ከጊዜ በኋላ በመገናኛው ድንኳን አጠገብ ካህናት የሚጠቀሙባቸው ሌሎች ክፍሎችም ሳይጨመሩ አልቀሩም። ሳሙኤል የሚተኛው ከእነዚህ ክፍሎች በአንዱ ውስጥ ይመስላል።