የግርጌ ማስታወሻ
b ዘሌዋውያን 19:18 “ወገንህን አትበቀል፤ ወይም ምቀኛ አትሁንበት፤ ነገር ግን ባልንጀራህን እንደ ራስህ ውደድ” ይላል። የአይሁድ ሃይማኖት መሪዎች “ወገንህ” እንዲሁም “ባልንጀራህ” የሚሉት አባባሎች የሚያመለክቱት አይሁዳውያንን ብቻ እንደሆነ ያምኑ ነበር። ሕጉ እስራኤላውያን ከሌሎች ብሔራት የተለዩ እንዲሆኑ ያዝዝ ነበር። ያም ሆኖ በመጀመሪያው መቶ ዘመን የነበሩት የሃይማኖት መሪዎች የሚያስፋፉትን አይሁዳውያን ያልሆኑ ሰዎች በሙሉ ጠላት በመሆናቸው በግለሰብ ደረጃ ሊጠሉ ይገባል የሚለውን አመለካከት አይደግፍም።