የግርጌ ማስታወሻ
a ጳውሎስ የወይራውን ዛፍ ሥጋዊ እስራኤላውያንን ለማመልከት እንደ ምሳሌ አልተጠቀመበትም። የእስራኤል ብሔር ነገሥታትና ካህናት የነበሩት ቢሆንም ብሔሩ የመንግሥት ካህናት አልሆነም። በሙሴ ሕግ መሠረት የእስራኤል ነገሥታት ካህናት መሆን አይችሉም ነበር። በመሆኑም የወይራው ዛፍ ለዚህ ብሔር ተምሳሌት ሊሆን አይችልም። ጳውሎስ ይህን ምሳሌ የተጠቀመው አምላክ “የመንግሥት ካህናት” ለማስገኘት ያለው ዓላማ ከመንፈሳዊ እስራኤል ጋር በተያያዘ ፍጻሜውን የሚያገኘው እንዴት እንደሆነ ለማስረዳት ነው። ይህ በነሐሴ 15, 1983 መጠበቂያ ግንብ (እንግሊዝኛ) ከገጽ 14-19 [መ.ግ. 8-104 ከገጽ 8-10] ላይ በወጣው ትምህርት ላይ የተደረገ ማስተካከያ ነው።